Back to Top
Holy Pictures of Orthodox Tewahedo Churchቅዱሳን ስዕላት Screenshot 0
Holy Pictures of Orthodox Tewahedo Churchቅዱሳን ስዕላት Screenshot 1
Holy Pictures of Orthodox Tewahedo Churchቅዱሳን ስዕላት Screenshot 2
Holy Pictures of Orthodox Tewahedo Churchቅዱሳን ስዕላት Screenshot 3
Free website generator for mobile apps; privacy policy, app-ads.txt support and more... AppPage.net

About Holy Pictures of Orthodox Tewahedo Churchቅዱሳን ስዕላት

This APP contains more than 400 different Holy Pictures of Ethiopian Orthodox Tewahedo Church Holy Saints, Holy Angels, Holy Fathers, Holy Mothers, and Holy Pictures of God with a List of Yearly, Monthly Holy Days which are celebrated in Orthodox Tewahedo Church and finally the app contains a list of biblical name and their meninges.

Please give attention that the Holy pictures which are found in this app are not the only one there are a lot of Saints which are not included in this APP.

በዚህ መተግበሪያ ውስጥ ከ400 በላይ የቅዱሳን ስዕላትን በማንኛውም ጊዜ ማግኘት እንዲችሉ ካለ ኢንተርኔት እንዲሰራ በመተግበሪያው ውስጥ ስእላቱ እንዲካተቱ ተደርጎዋል፡፡
ከቅዱሳኑ በረከት ረድኤት ይደርብን
አሜን!!!

ከዚህ በታች ያለው አቡነ ገብርኤል በ1990 ካሳተሙት “ክብረ ቅዱሳን» ከሚለው መጻሕፍ የተወሰደ ነው

የጥንቱና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የሚከተል ክርስቲያን ሁሉ ከቅዱሳት ሥዕሎች ሁለት ዐበይት ጥቅሞችን ያገኛል ይኽውም ትምህርትና ረድኤት ናቸው። ይልቁንም ዓለም ከመፈጠሩ በፊት የነበረው ቃለ እግዚአብሔር (አካላዊ ቃል) በኋለኛው ዘመን ሰውን ለማዳን ወደዚህ ዓለም መጥቶ ከቅድስት ድንግል ማርያም በድንግልና ተፀንሶ ከሥጋዋ ሥጋን ፣ ከነፍስዋ ነፍስን ነስቶ ከኃጢአት ብቻ በቀር ፍጹም ሰው ሆኖ በድንግልና የተወለደውና ተሰቅሎ በሞቱ ዓለሙን ማዳኑን በሥዕል ገልጾ ማቅረብ መስበክ፤ ማስተማር ነው። በዚህም መሠረት የጌታችንን የልደቱን ታሪክ፣ የጥምቀቱን ታሪክ፣ የስቅለቱን ታሪክ፣ የትንሣኤውንና የዕርገቱን ታሪክ በሥዕል ነድፎ ለምእመናን ማቅረብ ማለት የጌታችንን ወንጌለ መንግሥት መስበክና ማስተማር ማለት ነው ምክንያቱም ሥዕል ራሱበጉልህ የተጻፈ ጽሑፍ ማለት ነውና። ጌታችን ተወለደ፣ ተጠመቀ፣ ተሰቀለ ፣ ሞተ፣ ከሙታን ተለይቶተነሣ… የሚለው የወንጌሉ ታሪክ በሥዕል ማቅረብ ማለት ታሪኩን በጉልህ ጽፎ ማቅረብ ማለት ነው።
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ለገላትያ ክርስቲያኖች ተግሳጽ ሲጽፍ «የማታስተውሉ የገላትያ ሰዎች ሆይ፤ በዓይናችሁ ፊት ኢየሱስ እንደተሰቀለ ሆኖ ተሥሎ ነበር» ያለው ኢየሱስና ታሪኩን በሚገባ አውቀውትና ከልብም ተረድተውት እንደ ነበር ለመግለጽ ነው (ገላ.3፤ 1-2)

ስለዚህ ከላይ እንደተገለጸው ቅዱሳት ሥዕሎች በመመልከትና ልብ ብሎ በማንበብ (በማስተዋል) ታሪኩን በሚገባ ማወቅና መረዳት ስለሚቻል ፤ ስለዚህ በቤተ ክርስቲያን የሚገኙ ሥዕሎች የክርስትና ሃይማኖት አስተማሪዎችና አስረጂዎች መሆናቸውን መገንዘብ ተገቢ ነው።

ሁለተኛው ጥቅም ከቅዱሳት ሥዕሎች የሚገኘው ሌላው ዐቢይ ጥቅም ደግሞ ረድኤት (ርዳታ) ነው።

ኢየሱስ ክርስቶስ በነበረበት በጣም ቅርብ የነበሩት የጥንት ክርስቲያኖች በጌታችን ሥዕል፣ በቅድስት ድንግል ሥዕልና በቅዱሳን ሥዕሎች ይማፀኑ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ይመሰክራል ። በዘመናችን ተቆፍረው የተገኙ የጥንት አብያተ ክርስቲያናት ፍርስራሶችም በሥዕላተ ቅዱሳን መማፀን ጥንታዊ ትውፊት (ሥርዓት) እንደሆነ ያመለክታሉ ታሪክን መካድ ደግሞ አያትና ቅድመ አያትን መካድ ማለት ነው። ስለ ሥዕል ክብር የቤተ ክርስቲያን ትውፊታዊ ታሪክ ምስክር ነው። የታወቀው ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊ አውሳብዮስ ኤጲስ ቆጶስዘቂሳርያ ስለ ጌታ ሥዕል አጀማመርና አመጣጥ ጽፎ ያቀረበውን ብፁእ አባ ጎርጎርዮስ ሊቀ ጳጳስ ዘሸዋበመጽሐፋቸው ጠቅሰውታል። አኛም የጥቅሱን ፍሬ ነገር ቀጥለን ጠቅሰነዋል።

«ንጉሥ ዐብጋር በዑር (ኤዴሣ ከተማ የአገሩ ንጉሥ በመሆን ጌታችን በነበረበት ዘመን ይኖር ነበረ፤ ስሙም (ልዑካን) ይባል ነበር። ዐብጋር ማለት በከለዳውያን ቋንቋ ቄሣር ማለት ነው። ዐብጋር በዚያ ዘመን በጠና ታሞ ነበር፤ የጌታችንን ተአምራት በዝና ሰምቶ ይፈውሰው ዘንድ ደብዳቤ ጽፎ ለጌታችን ላከለት፤ ጌታችንም ደብዳቤውን ከመልእክተኛው እጅ ተቀብሎ ካነበበው በኋላ «ሳያየኝ ያመነኝ ዐብጋር ብፁዕ ነው» ብሎ ዐብጋርን በማመስገን በሱ ስም እንዲፈውሰው ከደቀ መዛሙርቱ መካከል አንዱን እንደሚልከለት በመግለጽ መልስ ላከለት። ነገር ግን ከጌታ ጋር ተገናኝቶ የተመለሰው የዐብጋር (ዩካማ) መልእክተኛ ሠዓሊ ስለነበር ከጌታችን ጋር ሲነጋገር ፊቱን በሥዕል ነድፎ (ሥሎ) ከደብዳቤው ጋር ይዞ ተመለሰ። ከዚያም አንደ ደረሰ ከጌታ የተላከውን ደብዳቤ ለታመመው ንጉሥ አነበበለት፤ ሥዕሉንም አሳየው። በዚያን ጊዜ በሽተኛው ንጉሥ የጌታችንን ቃል ከደብዳቤው ሰምቶና ሥዕሉንም በዓይኑ ተመልክቶ ወዲያው ከሕመሙ እንደ ተፈወሰ ታሪኩ ያስረዳል (አባ ጎርጎርዮስ፤ የኢ ኦ ተ ቤተ ክርስቲያንታሪክ 1974 ገጽ 119 120)።

ይኽው አውሳብዮስ ስለ ጌታችን ሥዕል የሰጠው ምስክርነት እንዲህ የሚል ነው «ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዕለተ ዓርብ ደሙን እያንጠፈጠፈ መስቀሉን ተሸክሞ ወደ ጎልጎታ በሚጓዝበት ወቅት እያለቀሱ ከሚከተሉት ደጋግ ሴቶች መካከል ቬሮኒካ የተባለች ደግ ሴት የራስዋን መሸፈኛ አውልቃፊቱን አንዲያድፍበት (እንዲጠርግበት ስጌታ ወረወረችለት፤ ጌታችንም በደምና በላብ የተጠመቀውን ፊቱን ጠርጎ ሲመልስላት ሥዕለ ገጹ ማለት የፊቱ መልክ በሻሽዋ ላይ ታትሞ ቀረ» በማለት ከላይ የጠቀስነው የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊው አውሳብዮስ ይመሰክራል።

ስለ ቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ደግሞ ወላዲተ አምላክ በነበረችበት ክፍለ ዘመን የነበረው ሐዋርያው ቅዱስ ያዕቆብ የጌታን ታሪክ (ወንጌል) ሲጽፍ ስለ ወላዲተ አምላክም ብዙ ጽፎአል። በዚህ የያዕቆብ ወንጌል (ያዕቆብ ታሪክ) በተባለው የትውፊት መጽሐፍ ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ለመጀመሪያ ጊዜ የማርያምን ሥዕል መሃሉ ተጽፎአል።

አውሳብዮስ ኤጲስ ቆጶስ ዘቂሳርያና ሌሎችም የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊዎች እንደ መሰከሩት የጥንትዋ ቤተ ክርስቲያን ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሥዕል ፣ ለወላዲተ አምላክ፣ ለቅዱሳን መላእክት፣ ለጻድቃንና ለሰማዕታት ሥዕሎች ከፍ ያለ ክብር እንዲደረግላቸውና የጸጋና የአክብሮት ስግደት እንዲቀርብላቸው ስታስተምር ኖራለች። ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን ትምህርት መሠረት በሚጸልዩበት ቤተ ክርስቲያንና በቤታቸው በሚገኘው በግል ጸሎት ቤታችው የጌታችንን፣ የቅድስት ድንግል ማርያምና የቅዱሳንን ሥዕሎች በግድግዳው በመስቀልና የክብር ስግደት በማቅረብሲማፀኑባቸው ኖረዋል።

በዚሁ ሁኔታ የሥዕል ክብር በጥንትዋ ቤተ ክርስቲያን እንደ ተጠበቀ አስከ ስምንተኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ድረስ ከቆየ በኋላ ሳይታሰብ በድንገት ከክርስቲያኖቹ መካከል ጥቂቶች ሰዎች የሥዕልን ክብር በመቃወም ተነሡ። በዚሁ ምክንያት በሮምና በቢዛንታይን ግዛቶች ከባድ ክርክርና ሁከት ተቀሰቀሰ። በዚህ ጊዜ በ797 ዓም የምስራቅቤተ ክርስቲያን መሪዎች ጉባዔ አድርገው የቅዱሳንን ሥዕሎችማክበርና መሳም(መሳለም) እንደሚገባ ለሥዕሎቹም የአክብሮት ስግደት ማቅረብ ተገቢ መሆኑን በሰፊው አትተው ወስነዋል... ቀሪውን ከዌብሳይቱ ላይ ያንብብቡ

Similar Apps

Ethiopian Bible Versesወሳኝ ጥቅሶች

Ethiopian Bible Versesወሳኝ ጥቅሶች

3.2

ይህ Ethiopian Bible መፅሃፍ ቅዱስ Verses in Amharic and English መተግበሪያ ከመፅሐፍ...

EthioSafari  (ሳፋሪኮም + ቴሌ)

EthioSafari (ሳፋሪኮም + ቴሌ)

0.0

App for Ethiopian Telecom users: EthioSafari (Safaricom + EthioTelecom) App supports both...

EthioTelecom + Amole (ቴሌና አሞሌ)

EthioTelecom + Amole (ቴሌና አሞሌ)

4.5

“Ethiopian Telecom in Easy Mode ኢትዮ ቴሎኮምን በቀላሉ” is rebranded to “Etel...

ስንክሳር * Sinksar Saints History

ስንክሳር * Sinksar Saints History

4.8

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን! ስንክሳር ማለት የእግዚአብሔርን ረድኤት...

ደላላ | Delala | Broker | Agent

ደላላ | Delala | Broker | Agent

0.0

ከሁለቱ ውጪ ሊሆኑ አይችሉም ወይ ደላላ ኖት ወይ ደግሞ ደላላ ያስፈልጎታል። ከዚህ...

መፅሃፍ ቅዱስ ለልጆች Children's Bible

መፅሃፍ ቅዱስ ለልጆች Children's Bible

0.0

ይህ በአማርኛ የቀረበ የመፅሃፍ ቅዱስ የመጀመሪያዎቹን ከፍጥረት ታሪክ እስከ ወንድማማቾቹ ያዕቆብ እና...

author
Contnue I it
haylies abedom
author
Egziabeher yemesgen tebarku
አይናችን ነሽ ማርያም
author
Nice
Yony Boy
author
Thank you beautiful pictures.
A.M.E
author
GOD bless you it is better if you type the name of saints
Soruma Gebeyehu
author
እግዚአብሔር ከዚህ በላይ ጥብብ ይስጥችሁ
Tasfey Barhnu